በቴክኖሎጂ በመታገዝ ተግባራትን አልቆ መፈፀም አንዱ የፓርቲያችን የትኩረት አቅጣጫ ነው !
" በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ማስተባበሪያ ዘርፍ የከተማ እና የክ /ከተማ ኃላፊዎች ያለፉትን ስድስት ወራት የስራ አፈፃፀም በመገምገም የዘርፉን የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች የጋራ አድርገዋል። በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ማስተባበሪያ ዘርፍ ኃላፊ አቶ መሀመድ አብዱልረሂም በውይይቱ ላይ እንደተናገሩት ጠንካራ ፓርቲ ለመገንባት ለሚደረገው ርብርብ የቴክኖሎጂን አቅም በአግባቡ መጠቀም ወሳኝ በመሆኑ ተግባራዊ የሚደረጉ አዳዲስ የቴክኖሎጂ ስራዎች ላይ በቂ ግንዛቤ እንዲያዝ የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። የተገኙ ውጤቶች በጥረታችን እና በልፋታችን የመጡ ናቸው ያሉት ኃላፊው ጉድለቶቻችን ላይ በመረባረብ ተጨባጭ ስኬቶችን ማበራከት ይገባል ብለዋል። ጊዜንና ወጪን በማያባክን መልኩ መረጃዎችን ለመለዋወጥ ኦንላይን ኮንፈረንስ ሲስተም በሁሉም ክ /ከተሞች በቅርቡ ወደ ተግባር እንደሚገባ ያመላከቱት አቶ መሀመድ በሁሉም የፓርቲ ወረዳዎች ቨርፑዋል ኮኔክቲቪቲን ለማጠናከር ርብርብ እንደሚደረግም አስገንዝበዋል። የአባላትንና የአመራሩን መረጃ በየጊዜው ማጥራትና ማዘመን፣ አዳዲስ አባላትን ወደ ዳታ ቤዝ ማስገባት ፣ የተንጠባጠቡ ስራዎችን ፈጥኖ ማስተካከል በልዩ ርብርብ ማከናወን እንደሚገባ ያስረዱት አቶ መሀመድ ከህዝብ ግንኙነት እና ሚዲያ ዘርፍ ጋርም የጋራ ስራዎችን ለማጠናከር ቅንጅታዊ ጥረት እንደሚደረግ አመላክተዋል። የየካ ክ/ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ ፅ / ቤት የፓለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ተራማጅ ተረፈ በውይይቱ ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት የካን የከፍታ ማሳያ ማድረግ የሚያስችሉ ለሀገራችንም ለከተማችም ማንሰራራት ጉልህ ፋይዳ ያላቸው የህዝባችንን የኑሮ ደረጃ የሚያሻሽ...